በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር አባል ጃል ሰኝ ነጋሳ ከድርጅቱ መነጠላቸውን አስታወቁ


የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር አባል ጃል ሰኝ ነጋሳ፣ ጃል መሮ(ኩምሳ ድሪባ)
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር አባል ጃል ሰኝ ነጋሳ፣ ጃል መሮ(ኩምሳ ድሪባ)
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር አባል ጃል ሰኝ ረጋሳ ከድርጅቱ መነጠላቸውን አስታወቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:29 0:00

በጃል መሮ ወይም ኩምሳ ድሪባ ከሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ራሳችንን አግልለናል ሲሉ የድርጅቱ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የማዕከላዊ ዞን የቀድሞ አዛዥ ጃል ሰኝ ነጋሳ አስታውቀዋል።

ጃል ሰኝ ነጋሳ መሆናቸውን ያስተዋወቁት የድርጅቱ አመራር፣ ከተመረጡ መገናኛ ብዙሀን ዘጋቢዎች በስልክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የት እንደሆኑ ባልተገለፀ ቦታ ሆነው በሰጡት ምላሽ፣ ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም የወጣውና የማዕከላዊ ዞን ዕዝ፣ በጃል መሮ ወይም ኩምሳ ድሪባ ከሚመራው ቡድን መለየቱን የሚገልፀው መግለጫ፣ የእሳቸውና የቡድናቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በኦሮሚያ የቀጠለውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ ነን ሲሉም ጃል ሰኝ ትናንት መሰከረም 16 ቀን 2017 በሰጡት በዚሁ መግለጫ ተናግረዋል።

በጉዳዩ ላይ ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አዛዥ ጃል መሮ ወይም ኩምሳ ድሪባ እና ባልደረቦቻቸው ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG