ለዚህ ምክንያቱ ምንድነው? ችግሩን እንዴት መፍታት ይቻላል? በሚለው ላይ ለመወያየት ስመኝሽ የቆየ በአሜሪካ የመድሃኒት ቁጥጥር አስተዳደር መስሪያ ቤት ውስጥ በፔዲያትሪክ ፋርማኮሎጂስትነት የምታገለግለውን ዶክተር ሊሊ ሙሉጌታ እና የማህበረሰብ ጥናት ባለሙያ እና በአፍሪካ ዲያስፖራ ማህበረሰብ ኮሌጅ ተደራሽነት ዙሪያ የሚሰራ ተቋም መስራች ማቲዮስ መስፍንን ስቱዲዮ ጋብዛ አነጋግራለች።
ራሳቸውን የሚያጠፉ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወጣቶች ቁጥር ለምን ጨመረ?
አሜሪካ ውስጥ በየ11 ደቂቃው አንድ ሰው ራሱን እንደሚያጠፋ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ መስሪያቤት መረጃ ያሳያል። ባለፈው ዓመት ብቻ ወደ 50 ሺህ የሚጠጉ አሜሪካውያን ራሳቸውን አጥፍተዋል። በተለይ እድሜያቸው ከ10 - 24 ዓመት ባሉ ወጣቶች ዘንድ ዋና የሞት መንስዔ መሆኑንም ተመልክቷል። ይህ ቁጥር ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወጣቶችንም ያጠቃልላል። ቁጥሩ በጥናት ባይረጋገጥም፣ ራሳቸውን የሚያጠፉ ኢትዮጵያዊ አሜሪካውያን ወጣቶች ቁጥር እየጨምረ መሄዱን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 10, 2025
የአሜሪካ ታጋቾች ተደራዳሪ ከሐማስ ጋራ የነበራቸውን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል
-
ማርች 09, 2025
"ከከተሞች ውጭ ያሉ አካል ጉዳተኞችም ትኩረትን ይሻሉ" - ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ
-
ማርች 09, 2025
አትሌቶችን በማፍራት ያለእድሜ ጋብቻን የሚከላከለው ተቋም
-
ማርች 09, 2025
የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት ለማሻሻል ያለመችው ወጣት
-
ማርች 08, 2025
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማርች 8ትን በሴቶች ብቻ በሚደረጉ በረራዎች እያከበረ ነው