በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በምዕራብ ጎንደር ዞን በቀጠለው እገታ እና ግድያ ከባድ ስጋት ላይ መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለጹ


በምዕራብ ጎንደር ዞን በቀጠለው እገታ እና ግድያ ከባድ ስጋት ላይ መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:51 0:00

በምዕራብ ጎንደር ዞን በመተማ ወረዳ እና አካባቢው በታጣቂዎች በቀጠለው ግድያ እና እገታ የተነሳ ወጥቶ ለመግባት መቸገራቸውን እና ከፍተኛ የደኅንነት ስጋት እንዳደረባቸው ነዋሪዎች ለቪኦኤ ገልጸዋል፡፡

ባለፈው ሳምንት ረቡዕ፣ ከጎንደር ወደ መተማ በሚወስደው መንገድ ልዩ ስሙ "መቃ" በተባለ ሥፍራ፣ ታጣቂዎች በአንድ የሕዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ታክሲ ላይ ባደረሱት ጥቃት፣ ሾፌሩን ጨምሮ ሦስት ሰዎች ሲገደሉ፣ 14 ሰዎች ታግተው ወደ ጫካ እንደተወሰዱ የተጎጂዎች ቤተሰቦች ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

በጉዳዩ ላይ፣ ከዞኑም ኾነ ከወረዳው ባለሥልጣናት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በዐማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች፣ በተለይ ለማስለቀቂያ ቤዛ ገንዘብ ሲባል የሚፈጸሙ ሲቪል ሰዎችን ዒላማ ያደረጉ እገታዎች አሳሳቢ መኾናቸውን ጠቅሶ ተገቢው ትኩረት እንዲሰጣቸው፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ ባወጣው የ2016 ዓ.ም. ሦስተኛ ዓመታዊ ሪፖርቱ ማሳሰቡ ይታወሳል።

XS
SM
MD
LG