በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሱዳናውያን ስደተኞችን በዐማራ ክልል የማዛወር ጥረትን አሜሪካ እንደምትደገፍ ገለጸች


ሱዳናውያን ስደተኞችን በዐማራ ክልል የማዛወር ጥረትን አሜሪካ እንደምትደገፍ ገለጸች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:18 0:00

ዩናይትድ ስቴትስ፣ በዐማራ ክልል የሚገኙ ሱዳናውያን ስደተኞችን፣ በክልሉ ወደሚገኝ ወደ ዐዲስ ቦታ ለማዛወር የተጀመረውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ፣ በስደተኞች ላይ የሚደርሰው ማንኛውንም ጥቃት እንዲቆም አሳስቧል፡፡

በምዕራብ ጎንደር ዞን ውስጥ ባሉት ሁለት የመንግሥታቱ ድርጅት የመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሱዳናውያን ስደተኞችን በዞኑ ወደሚገኝ ሌላ ቦታ ለማዛወር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ቦታ ማዘጋጀቱን፣ በስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት የኩመር፣ የአውላላ እና የዓለምዋጭ መጠለያ ጣቢያዎች አስተባባሪ አቶ ታምራት ደምሴ ተናግረዋል፡፡

የስደተኞቹ ጉዳይ እንደሚያሳስበው የሚገልጸው የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በበኩሉ፣ በኢትዮጵያ ላሉ የሱዳን ስደተኞች ከዓለም አቀፍ ለጋሾች የሚቀርበው ድጋፍ እጅግ አነስተኛ መኾኑን አመልክቷል፡፡

በዐማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙ ሱዳናውያን ስደተኞችን ደኅንነት ለማረጋገጥ፣ በዞኑ ወደሚገኝ ዐዲስ ቦታ ለማዛወር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እና የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በምኅጻሩ-ዩኤንኤችሲአር የጀመሩትን ጥረት እንደምትደግፍ ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቃለች፡፡

XS
SM
MD
LG