በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“የመንግሥት ኀይሎች በዐማራ ክልል የጤና ተቋማት ላይ ከጦር ወንጀል የሚቆጠር ጥቃት አድርሰዋል” - ሂውማን ራይት ዋች


በዐማራ ክልል፣ በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች እና በፋኖ ታጣቂ ቡድኖች መካከል በመካሔድ ላይ ባለው ግጭት፣ በጤና ተቋማት እና በሠራተኞቻቸው እንዲሁም በታካሚዎች ላይ፣ “እንደ ጦር ወንጀል የሚቆጠር” ሰፊ ጥቃት መፈጸሙን፣ ዛሬ ረቡዕ ይፋ የኾነው የሂውማን ራይትስ ዋች ሪፖርት አስታውቋል።

የድርጅቱ የአፍሪካ ምክትል ዲሬክተር ላቲሺያ ባድር፣ “የኢትዮጵያ ኀይሎች አንዳችም ተጠያቂነት በሌለበት ኹኔታ፣ በዐማራ ክልል በጤና ተቋማት እና በጤና ሠራተኞች የጦር ወንጀል በሚባል ደረጃ ጥቃት ፈጽመዋል፤” ሲሉ ከሰዋል። ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቱ ሂውማን ራይትስ ዋች፣ ዛሬ ረቡዕ ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ፣ ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ጀምሮ፣ በዐማራ ክልል በሚገኙ ቢያንስ 13 ከተሞች፣ በፌዴራል ኀይሎች እና በፋኖ ታጣቂ ቡድኖች መካከል በቀጠለው ግጭት፣ በሕክምና መስጫ ተቋማት እና በሠራተኞቻቸው፣ እንዲሁም በታካሚዎች እና በመጓጓዣ አገልግሎቶች ላይ፣ በኢትዮጵያ የጸጥታ ኀይሎች እና በመንግሥት በሚደገፉ ሚሊሺያዎች፣ እንደ ጦር ወንጀል የሚቆጠር ጥቃት በስፋት መፈጸሙን አትቷል፡፡

XS
SM
MD
LG