ኢትዮጵያ፣ ወጣት ጥፋተኞችን በተመለከተ ሊፈጸሙ የሚገቡ ልዩ ሕጎችንና ደንቦችን ብታወጣም በቅጡ ባለመተግበራቸው፣ አዳጊዎች ከጥፋታቸው ተምረው፣ ሕይወታቸውን ሊያስተካክሉ የሚችሉበትን ዕድል እየተነጠቁ ስለመኾኑ በተደጋጋሚ ይነገራል።
ይህን ኹኔታ ለመቀየር ያለመው “የሕግ ባለሞያዎች ለሰብአዊ መብቶች” የተሰኘው ተቋም፣ የፍትሕ ሒደት ተዋንያንን የዕውቀት እና ግንዛቤ ውስንነነት ለማስፋት ጥረት ጀምሯል።
ተቋሙ፣ ሰሞኑን ከአካሔዳቸው እንቅስቃሴዎች ስለ አንዱ የሚያወጉንን እንግዳ ሀብታሙ ሥዩም አነጋግሯል።
እንግዳችን፥ በተቋሙ የስልታዊ ሙግት አስተባባሪ ሜሮን ተስፋዬ ናቸው።
አስቀድመው በኢትዮጵያ ሕጎች መሠረት ወጣት ጥፋተኞች ተብለው የሚገለጹ ዜጎችን ማንነት ያስረዱናል።