በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ተካሔደ


በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ተካሔደ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:32 0:00

በኢትዮጵያ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ጨምሮ በአራት ክልሎች፣ ትላንት እሑድ፣ የስድስተኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ መካሔዱን፣ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኀይሉ፣ የምርጫውን መጠናቀቅ አስመልክተው፣ ትላንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ምርጫው፥ በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች መከናወኑን ተናግረዋል።

በጸጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ያልተካሔደባቸው 40 የምርጫ ጣቢያዎችም እንዳሉ ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

ምርጫው በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ሲካሔድ፣ ከ10 ዓመታት በኋላ እንደኾነ ያመለከተው የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ሕዝቡ የሚፈልገውን መሪ ለመምረጥ ዕድል መስጠቱን ጠቅሶ፣ ሒደቱም በሰላም መጠናቀቁን ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቋል፡፡

XS
SM
MD
LG