በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጉጂ ዞኖች ግጭት አሠቃቂ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ ተባብሶ መቀጠሉን ካርድ አስታወቀ


በጉጂ ዞኖች ግጭት አሠቃቂ የሰብአዊ መብቶች ረገጣ ተባብሶ መቀጠሉን ካርድ አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:52 0:00

በሁለቱ የጉጂ ዞኖች ለዓመታት በቀጠለው ግጭት ሳቢያ፣ አሠቃቂ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እየተፈጸመ መኾኑን የገለጸው የመብቶች እና የዴሞክራሲ እድገት ማዕከል በምኅጻሩ ካርድ፣ ለዞኖቹ ነዋሪዎች የሰላም፣ የፍትሕ እና የተጠያቂነት ርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ አቀረበ፡፡

የመብቶች ተሟጋቹ፣ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ፣ በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች እና በታጣቂዎች መካከል ለዓመታት እንደዘለቀ በገለጸው “ነውጥ አዘል ግጭት” ሳቢያ፣ በዞኖቹ ነዋሪዎች ላይ የደረሱ ሠቆቃዎችን ያሳያሉ ያላቸውን 36 የማሳያ ታሪኮች በጥናታዊ ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል፡፡

ሁለቱን የጉጂ ዞኖች ጨምሮ በኦሮሚያ ምዕራባዊ ዞኖች፣ በትግራይ፣ በዐማራ እና በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልሎች በቀጠሉ ግጭቶች እና ግጭቶቹ ባስከተሏቸው ጫናዎች፣ አዎንታዊ ለውጥ ይመጣል ብሎ እንደማያምን የገለጸው ካርድ፣ ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት፥ ሐቀኛ እና አሳታፊ ድርድሮች እንዲደረጉ፣ በነውጥ አዘል ግጭቶች ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ፍትሕ እንዲያገኙ፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ተጠያቂ እንዲኾኑ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥሪ አቅርቧል፡፡

በኦሮሚያ ክልል በጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች፣ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እና በመንግሥት የጸጥታ ኀይሎች መካከል ለዓመታት በቀጠለው ግጭት፣ የዜጎች መደበኛ ሕይወት መቋረጡን የገለጸው የመብቶች እና የዴሞክራሲ እድገት ማእከል በምኅጻሩ ካርድ፣ በዞኖቹ ነዋሪዎች ላይ ይፈጸማሉ ባላቸው አሠቃቂ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ላይ ያካሔደውን ጥናታዊ ሪፖርት፣ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ይፋ አድርጓል፡፡

XS
SM
MD
LG