በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ጸደቀ


ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ጸደቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:20 0:00

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ በዐመፅ ተግባር ላይ ተሳትፈዋል የተባሉ ፓርቲዎች ዳግም ሕጋዊ እውቅና እንዲያገኙ የሚያስችል የዐዋጅ ማሻሻያ ዛሬ አፀደቀ።

የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶር. ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ ዐዋጁ አገራዊ ምክክሩን ታሳቢ በማድረግ መሻሻሉን ገልጸዋል፡፡ በዚኽም፣ ህወሓት እና በዐመፅ ተግባር ሲሳተፉ ነበሩ የተባሉ ፓርቲዎችን፣ እንዲሁም በትጥቅ ግጭት ውስጥ ያሉ ቡድኖችን ወደ ምክክር ሒደቱ ለማምጣት መታለሙን ተናግረዋል፡፡ በዐዋጁ ማሻሻያ ላይ፣ ከምክር ቤት አባላት የድጋፍ እና የተቃውሞ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል፡፡

XS
SM
MD
LG