በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኪረሙ ወረዳ ተመላሽ ተፈናቃዮች በመሠረታዊ አቅርቦቶች መቸገራቸውን ገለጹ


የኪረሙ ወረዳ ተመላሽ ተፈናቃዮች በመሠረታዊ አቅርቦቶች መቸገራቸውን ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:45 0:00

በምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ፣ ባለፉት ዓመታት በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ተፈናቅለው የነበሩ ከ52ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ወደ ቀዬአቸው መመለሳቸውን፣ የዞኑ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት(ቡሳ ጎኖፋ) አስታውቀዋል፡፡

ተመላሾቹ በበኩላቸው፣ በቂ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸውና በመሠረታዊ አቅርቦት ችግር ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን(ቡሳ ጎኖፋ) ኃላፊ ሞገስ ኢዳኤ ደግሞ፣ ተፈናቃዮቹ በዚኹ ግንቦት ወር የምግብ ርዳታ እንደተደረገላቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

XS
SM
MD
LG