በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሱዳን ጥገኝነት ለጠየቁ የቀድሞ ሰላም አስከባሪዎች ጥበቃ እንደሚያደርግ የስደተኞች ተቋሙ ገለጸ


በሱዳን ጥገኝነት ለጠየቁ የቀድሞ ሰላም አስከባሪዎች ጥበቃ እንደሚያደርግ የስደተኞች ተቋሙ ገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:09 0:00

በሱዳን በጥገኝነት እየኖሩ ያሉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ አባላት፣ ተፋላሚው የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች"፣ በሰሞኑ መግለጫው ካቀረበው የጣልቃ ገብነት ክስ ጋራ ተያይዞ የደኅንነት ስጋት እንዳደረባቸው ገለጹ፡፡

ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን የትግራይ ተወላጅ የሰላም አስከባሪ አባላት፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች" ባወጣው መግለጫ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በሱዳኑ ጦርነት እየተሳተፉ እንደኾነ ያቀረበው ክስ፣ “በመጠለያ ጣቢያዎች ያለነውን ስደተኞች ለጥቃት እንዳይዳርገን ስጋት ፈጥሮብናል፤” ብለዋል፡፡

ስለ ጉዳዩ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል አስተያየት የሰጠው የተባበሩት መግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በበኩሉ፣ “የስደተኞቹን የደኅንነት ስጋት እረዳለኹ፤ ኹኔታውን የተመለከተ መፍትሔም እያፈላለግኹ ነው፤” ብሏል፡፡

XS
SM
MD
LG