በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፍርድ ቤት በእነቀሲስ በላይ መኰንን ላይ የክስ መመሥረቻ የ15 ቀን ጊዜ ሰጠ


ፍርድ ቤት በእነቀሲስ በላይ መኰንን ላይ የክስ መመሥረቻ የ15 ቀን ጊዜ ሰጠ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:17 0:00

ዐቃቤ ሕግ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ክስ ለመመሥረት የጠየቀው የ15 ቀን ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡

ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንንን ጨምሮ፣ ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከስድስት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት ሙከራ በማድረግ የተጠረጠሩት ሦስት ግለሰቦች፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ለሦስተኛ ጊዜ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ክርክር ተደርጓል፡፡

ዐቃቤ ሕግ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይንና አብረዋቸው የታሰሩ ሁለት ግለሰቦችን፣ በከባድ የሙስና ወንጀል መጠርጠሩን ለችሎቱ ገልጿል፡፡

የተጠርጣሪዎች ጠበቆች በበኩላቸው፣ ዐቃቤ ሕግ ተጨማሪ ጊዜ ሳያስፈልገው ክስ መሥርቶ መቅረብ እንደነበረበት ገልጸው፣ ደንበኞቻቸው በዋስ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡

የዛሬው ችሎት የተቀጠረው፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን፣ እንዲሁም ያሬድ ፍሥሓ እና ዳባ ገናና በተባሉ ሹፌራቸው እና አጃቢያቸው ላይ ምርመራ ለማጣራት፣ ፖሊስ ለሁለተኛ ጊዜ በፍርድ ቤቱ በተሰጡት ሰባት የምርመራ ቀናት ውስጥ ያከናወነውን ምርመራ ለመመልከት ነበር፡፡

መርማሪ ፖሊስ፣ ምርመራውን አጠናቆ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ መላኩን፣ በዛሬው ችሎት ላይ ገልጿል፡፡

XS
SM
MD
LG