በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአሜሪካ የወፍ ጉንፋን በሽታን ለማስቆም ተጨማሪ ላሞች እየተመረመሩ ነው


ፋይል - ካልፎርኒያ ውስጥ በሚገኘ የወተት ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙ ላሞች ምስል - ህዳር 23፣ 2016
ፋይል - ካልፎርኒያ ውስጥ በሚገኘ የወተት ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙ ላሞች ምስል - ህዳር 23፣ 2016

በዩናይትድ ስቴትስ እየተዛመተ የመጣውን ወረርሽኝ ለመረዳት እና ለማስቆም፣ የአሜሪካ የጤና እና የግብርና ባለስልጣናት በወተት ላሞች ላይ 'በርድ ፍሉ' የተሰኘውን የወፍ ጉንፋን በሽታ ምርመራ እያካሄዱ ነው።

ባለስልጣናቱ እስካሁን ወደ ሰዎች የመዛመቱ ስጋት ዝቅተኛ ነው ቢሉም፣ የሳይንስ ባለሙያዎች ግን ቫይረሱ በቀላሉ እራሱን ሊለውጥ እና ወደ ሰዎች ሊዛመት ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን እየገለፁ ነው።

A H5N1 የተሰኘው የቫይረስ አይነት በስምንት ግዛቶች ውስጥ በሚገኙ ወደ ሠላሳ የሚጠጉ የወተት ላሞች ውስጥ ተገኝቷል። የተዳከመ ወይም አቅም የሌለው የቫይረሱ ዝርያም ግሮሰሪ ውስጥ በሚሸጡ ወተቶች ውስጥ ተገኝቷል።

እስካሁን የተደረጉ ምርመራዎች የቫይረሱን ምልክት የማያሳዩትን ጨምሮ በላሞች መካከል እና በላሞች እና በወፎች መካከል እየተዛመተ መሆኑን አመልክተዋል ሲል፣ የዩናይትድ ስቴትስ የግብርና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አስታውቋል።

ከሰኞ ጀምሮ በመቶውች እና በሺዎች የሚቆጠሩ የሚያጠቡ ላሞች ወደተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ምርመራ ሊደረግላቸው እና ቫይረሱ እንደሌለባቸው ማረጋገጫ ሊሰጣቸው እንደሚገባ የፌደራል መንግስት አዲስ ትዕዛዝ አስጥቷል።

በአሁኑ ወቅት ፈልቶ የቀዘቀዘ ወተት መጠጣት ችግር እንደማያስከትል የገለፁት የጤና ባለሙያዎች፣ ሆኖም ህብረተሰቡ ያልፈላ ወተት ከመጠጣት መታቀብ እንዳለበት አስጠንቅቀዋል።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG