በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክሩ ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ እየጠየቁ ናቸው


ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክሩ ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ እየጠየቁ ናቸው
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:12 0:00

የፖለቲካ ፓርቲዎች ለአገራዊ ምክክር የሚሆኑ አጀንዳዎችን እንዲያዘጋጁ ኮሚሽኑ ጠይቋል፡፡ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በበኩላቸው፣ በሒደቱ ለመሳተፍ መተማመንን ያዳብራሉ ያሏቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡

ከቅድመ ሁኔታዎቹ መካከል፣ በፖለቲካ አመለካከታቸው የታሰሩና በምክክር ሒደቱ የጎላ ሚና ሊኖራቸው ይችላል ያሏቸው አካላት እንዲፈቱ የሚጠይቁ ይገኙበታል፡፡

ኮሚሽኑ በበኩሉ፣ ሒደቱ ኹሉንም አካላት ማሳተፍ ያለበት በመኾኑ፣ የፓርቲዎች ቅሬታ እልባት እንዲያገኝ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

XS
SM
MD
LG