በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ መንግሥት የባለድርሻዎችን ተሳትፎ በማሳደግ ቀውሶችን ለመፍታት ቃል ገባ


የኢትዮጵያ መንግሥት የባለድርሻዎችን ተሳትፎ በማሳደግ ቀውሶችን ለመፍታት ቃል ገባ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:22 0:00

በጄኔቫ በተደረገው የድጋፍ ማሰባሰቢያ ላይ ኹነኛ አስተዋፅኦ ሊያደርግ የሚችል ድጋፍ መገኘቱን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል።

ኾኖም በተደራራቢ ዓለም አቀፋዊ ግጭቶች ምክንያት የታቀደውን ያህል ድጋፍ አለመገኘቱን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ፣ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብሩን ተከትሎ የአውሮፓ ኅብረት ባወጣው መግለጫ፣ “በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የቀጠለው ግጭት እና በደል ለተጨማሪ የሕዝብ መፈናቀል ምክንያት መኾኑ አሳስቦኛል፤” ብሏል።

የጄኒቫው መርሐ ግብር አዘጋጆች በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት “የቀውሶችን ቁልፍ ቋጠሮዎች ለመፍታት ባለድርሻ አካላትን በንቃት ለማሳተፍ ቃል መግባቱን” አመልክተዋል፡፡

ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG