በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“አንድ ቢሊዮን ዶላር እስክናገኝ ጥሪያችንን እንቀጥላለን” - ዩኤንኦቻ


“አንድ ቢሊዮን ዶላር እስክናገኝ ጥሪያችንን እንቀጥላለን” - ዩኤንኦቻ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:00 0:00

በመጪዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ፣ በኢትዮጵያ የነፍስ አድን ርዳታ ለማቅረብ አንድ ቢሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ለዚሁ ዓላማ ትላንት ማክሰኞ፣ በስዊዘርላንድ - ጄኔቫ በተካሔደ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት፣ ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የተስፋ ቃል መገባቱን ገለጸ፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ ወይም በምኅጻሩ ዩኤን-ኦቻ ምክትል ቃለ አቀባይ ጀንስ ላርክ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ከጄኔቫ በሰጡት የስልክ ቃለ መጠይቅ፣ ገቢው የተገኘው ከ20 ለጋሾች መኾኑን ጠቅሰዋል፡፡ አስቸኳይ ርዳታ የሚያስፈልገው አንድ ቢሊዮን ዶላር እስኪገኝ ድረስም ጥሪ ማቅረባችንን እንቀጥላለን፤ ብለዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG