በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

​ሙሉቀን መለሰ አረፈ


​ሙሉቀን መለሰ አረፈ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:06 0:00

ሙሉቀን መለሰ ባደረበት ህመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ69 ዓመት ዕድሜው ትላንት ማረፉን አንድ የቤተሰቡ አባል ለአሜሪካ ድምጽ ገልፀዋል።

ሙሉቀን መለሰ እስካረፈበት ጊዜ ድረስ ላለፉት አርባ ዓመታት በዩናይትድ ስቴትስ በቪርጂንያ ግዛት ውስጥ ኖሯል።

በ1946 ዓ.ም. በጎጃም ጠቅላይ ግዛት አነደድ ወረዳ ልዩ ስሙ ዳማ ኪዳነ ምሕረት በሚባል መንደር የተወለደው ሙሉቀን በስድስት ዓመቱ ከአጎቱ ጋር ወደ አዲስ አበባ መምጣቱን የህይወት ታሪኩን የሚዘክር ጽሑፍ ይጠቁማል።

የ12 ዓመት አዳጊ ሆኖ በምሽት ክለቦችና በሙዚቃ ቡድኖች ውስጥ መዝፈን የጀመረው ሙሉቀን ከሁለት ዓመት የምሽት ክለቦች ቆይታ በኋላ በ1960 ዓ.ም. የፖሊስ ሠራዊት ኦርኬስትራን ተቀላቅሏል።

XS
SM
MD
LG