በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ራሳቸውን የሚያጠፉ ወጣቶች ቁጥር የመጨመር ምክኒያቶች እና መፍትሔዎች


ራሳቸውን የሚያጠፉ ወጣቶች ቁጥር የመጨመር ምክኒያቶች እና መፍትሔዎች
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:23 0:00

በዩናይትድ ስቴትስ ራሳቸውን የሚያጠፉና ራሳቸውን ለማጥፋት የሚሞክሩ ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ መሆኑን፣ የአሜሪካ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ማዕከል(CDC) መረጃ ያሳያል።

አመለካከቱና ድርጊቱ፣ በተለይ ዕድሜያቸው ከ10 እስከ 24 ዓመት በሆኑ ጥቁር ወጣቶች ዘንድ በዝቶ እንደሚታይ በመረጃው ተገልጿል፡፡ የዘር መድልዎ፣ የኢኮኖሚ ችግር፣ ድህነት፣ የትምህርት ዕድል ዕጦት፣ የጤና አገልግሎት ተደራሽ አለመሆንና ሌሎች ማኅበራዊ ችግሮች፣ የወጣቶቹ ራስን የማጥፋት መግፍኤዎች እንደሆኑ አመላክቷል።

የላስ ቬጋስ ዘጋቢያችን በከተማዋ በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ዘንድ እየጨመረ የመጣውን የራስን ሕይወት በገዛ እጅ የማጥፋት ችግር አስመልክቶ የሚመለከታቸውን አካላት አነጋግሮ ዘገባ ልኳል።

XS
SM
MD
LG