በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለስልታዊ እና ተደጋጋሚ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ኢሰመኮ ጠየቀ


ለስልታዊ እና ተደጋጋሚ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ኢሰመኮ ጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:47 0:00

በኢትዮጵያ የሚፈጸመው ስልታዊ እና ተደጋጋሚ የዘፈቀደ እስራት፣ ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያስፈልገው፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ።

ኢሰመኮ፣ ከሚያዝያ 2010 እስከ ሚያዝያ 2015 ዓ.ም. ባሉት አምስት ዓመታት “ነጻነታቸውን ተነፍገዋል፤” ባላቸው ሰዎች መብቶች ጉዳይ ባለ130 ገጽ የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ሪፖርቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡን የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ፣ በኢትዮጵያ የተለያዩ አገራዊ ዐውዶች እና ኹነቶች ውስጥ የተራዘመና የዘፈቀደ እስራት እንዲሁም በታሳሪዎችና በቤተሰቦቻቸው ላይ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በስፋት እንደሚፈጸም አስረድተዋል፡፡

በአገሪቱ አንጻራዊ መረጋጋት በሚኖርበት ጊዜ፣ በእስረኞች አያያዝና በማቆያ ስፍራዎች ላይ የተወሰኑ መሻሻሎች እንደታዩ የገለጹት ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ፣ በግጭት ወቅት ግን ይፈጸማሉ ያሏቸውን የመብቶች ጥሰቶች ለማስቆም ጠቃሚ ነው ያሉትን ምክረ ሐሳብ አቅርበዋል።

በመደበኛነት ከሚደረጉ የሰብአዊ መብቶች ምርመራዎች በተጨማሪ፣ ብሔራዊ ምርመራ ማድረግ አንዱ የምርመራ ሥነ ዘዴ እንደኾነ ኮሚሽኑ ጠቁሟል። ይኸውም፣ በስፋት እና በተደጋጋሚ ውስብስብ በኾነ መልኩ በሚፈጸሙ፣ ብዙዎችን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ሰለባ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መፍትሔዎችን ለማፈላለግ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡

ብሔራዊ ምርመራ በልዩ ልዩ ሀገራት የተለመደ መኾኑን የገለጹት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ፣ በኢትዮጵያ ምርመራው ሲደረግ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡

XS
SM
MD
LG