በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የብርና የነሃስ ሜዳሊያ አገኝች


በዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የብርና የነሃስ ሜዳሊያ አገኝች
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:11 0:00

ግላስኮ፣ስኮትላንድ ውስጥ ለሁለተኛ ቀን በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሁለት ሜዳሊያ አግኝታለች።  በሴቶች የ3ሺሕ ሜትር  የፍፃሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች።

በዚህ ውድድር የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን ሰብራ አሜሪካዊቷ ኤሌ ፔዬሬ የወርቅ፣ ኬኒያዊቷ አትሪስ ቼፕኮኤች ደግሞ የነሃስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።ኢትዮጵያውያኑ ለምለም ሃይሉ እና ሂሩት መሸሻ ስድስተኛ እና ሰባተኛ ደረጃን ይዘው ጨርሰዋል። በወንዶቹ የ3ሺሕ ሜትር ውድድር አትሌት ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አስገኝቷል። የታላቋ ብሪታኒያው አትሌት ጆሽ ኬር የወርቅ ሜዳሊያውን ሲወስድ፣ አሜሪካዊው ያሬድ ንጉሴ ደግም የብር ሜዳሊያ አስገኝቷኣል። በቡድን ሥራ ትልቁን ድርሻ የወሰደው አትሌት ጌትነት ዋለ አራተኛ በመውጣት የዲፕሎማ አግኝቷል:: ኤቢሳ ነገሰ ከስፍራው ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG