በጋዛው ጦርነት የረመዳን ጾም ከመግባቱ አስቀድሞ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ አደራዳሪዎች ብርቱ ግፊት እያደረጉ ይገኛሉ።
ሆኖም፣ 30ሺሕ የሚደርሱ ፍልስጥኤማውያን በተገደሉበት የእስራኤል የጋዛ ወታደራዊ ዘመቻ፣ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በሰጡት ድጋፍ ሳቢያ ከወደ ሚሽጋን የቁጣ መልእክት እየተሰማ ነው።
የመጪው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የቅድሚያ ውጤቶች እንደሚያሳዩት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አረብ አሜሪካውያን በሚኖሩባት የሚሽጋን ግዛት፣ በርካታ መራጮች በምርጫ ካርዳቸው ላይ “ድምፅ ያልሰጠ” የሚለውን ምልክት በማቅለም ለፕሬዚዳንት ባይደን ድምፃቸውን መንፈጋቸውን እያሳዩ ይገኛሉ።
ይህቺው የሚሽጋን ግዛት፣ አንድ ጊዜ የዴሞክራቱን እጩ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሪፐብሊካንን እጩ በመምረጥ በፕሬዝዳንታዊው የምርጫ ሒደት ወሳኝ ተደርጋ ትታያለች፡፡
የአሜሪካ ድምፅዋ የዋይት ሐውስ ቢሮ ኃላፊ ፓትሲ ዊዳኩስዋራ፣ ሌላዋ ዘጋቢያችን ዶራ መኩዋር ከሚሽጋን ያጠናቀረችውን አጣምራ ያደረሰችንን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ
-
ጁላይ 22, 2024
የነዋሪዎች አስተያየት በፕሬዝደንት ባይደን ውሳኔ ላይ
-
ጁላይ 18, 2024
ጄ. ዲ. ቫንስ “አሜሪካ ትቅደም” መሪ ቃላቸው እንደሆነ አስታወቁ