የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በጋምቤላ ክልል ከግንቦት 2015 እስከ ጥር 2016 ዓ.ም ድረስ በተከሠቱ ግጭቶች፣ ቢያንስ 138 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ፣ በግጭቱ የንብረት ውድመት እና ዘረፋ መፈጸሙንም በምርመራው ማረጋገጡን ጠቅሷል።
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አቤል አዳነ፣ ስለ መግለጫው ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ፣ በግጭቱ በጋምቤላ ክልል የሚኖሩ ስደተኞችም እንደተሳተፉ ተናግረዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጠው የክልሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በበኩሉ፣ ባለፈው ዓመት ከግንቦት እስከ ነሓሴ ወራት ድረስ አጋጥሟል ባለው ግጭት፣ በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት መድረሱን አምኖ፣ መጠኑን ግን አልገለጸም፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
በማላዊ ለአሳዳጊ አልባ ሕፃናት መጠጊያ የኾነው ማዕከል
-
ጁላይ 27, 2024
በጠፈር ምርምር ትምህርት መርሐ ግብር የተመረቁ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ