የምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኤኮዋስ) በኒዤር ላይ የጣለውን ማዕቀብ ማንሳቱ፣ እንዲሁም በማሊ እና ቡርኪና ፋሶ ላይ የነበረውን ማዕቀብ ላላ ለማድረግ መወሰኑ፣ በአብዛኛው የቀጠናው የፖለቲካ ተንታኞች ዘንድ በመልካም ታይቷል።
ኤኮዋስ እንደሚለው፤ ባለፈው ቅዳሜ የደረሰበት ውሳኔ፣ ሰብአዊነትን መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ በሦስቱ አገራት ካሉ ወታደራዊ ሁንታዎች ጋር ንግግር ለመጀመርም ጥርጊያ መንገድ ይከፍታል። አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ግን፣ የኤኮዋስ ውሳኔ ብዙም ውጤት አይኖረም ሲሉ ይተቻሉ።
ቲመቲ ኦቢይዙ ከአቡጃ የላከውን ዘገባ እንግዱ ወልዴ ወደ አማርኛ መልሶታል።