በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሞሊ ፊ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተወያዩ


ሞሊ ፊ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተወያዩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:13 0:00

የዩናይትድ ስቴትሷ ከፍተኛ ዲፕሎማት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ሰላምንና ጸጥታን ጨምሮ በኢትዮጵያ እና በአካባቢው ሀገራት ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ላይ ለመታደም ኢትዮጵያ የገቡት ሞሊ ፊ፣ ከኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ጋራም በሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡

የአህጉራዊ ኅብረቱ መቀመጫ የኾነችውን ኢትዮጵያንና አንዳንድ ጎረቤቶቿን ጨምሮ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በደኅንነት ቀውስ ውስጥ እያሉ የሚካሔደው የኅብረቱ ጉባኤ በአዲስ አበባ ቀጥሏል፡፡ የኅብረቱ መሪ ቃል ትምህርት ተኮር ቢኾንም፣ ጉባኤው በአህጉሪቱ ቀውሶች ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ እንደሚወያይ፣ የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር ገልጸዋል፡፡

አማርኛ የኅብረቱ ይፋዊ የሥራ ቋንቋ እንዲኾን፣ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ጠይቃለች፡፡ ለደኅንነቷም መጠናከር ከኅብረቱ እና ሌሎች አጋሮች ጋራ ለመሥራት ዝግጁ እንደኾነች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በአፍሪካ ኅብረት 37ኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ የሚገኙት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ፣ ትላንት ረቡዕ፣ የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋራ ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡

XS
SM
MD
LG