ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ አከፋፈል ለማስተካከል ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋራ እያደረገቻቸው ባሉ ድርድሮች፣ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም አንዱ ኢኮኖሚያዊ መፍትሔ ተደርጎ በምክረ ሐሳብ ደረጃ ስለመቅረቡ ይገለጻል፡፡ ምክረ ሐሳቡ ለዓመታት ሲቀርብ እንደቆየ ያወሱት የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት አማካሪው አቶ ያሬድ ኀይለ መስቀል፣ መንግሥት ግን ሳይስማማበት የቆየ ጉዳይ ስለመኾኑ ይናገራሉ፡፡ ይኹንና ባለፉት አምስት ዓመታት፣ ብሔራዊ ባንክ የወሰዳቸው የብርን የመግዛት አቅም የማዳከም ርምጃዎች፣ ከመፍትሔ ይልቅ ለዋጋ ንረት እና ተያያዥ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ዳርገዋል፤ ይላሉ፡፡ የምጣኔ ሀብት ባለሞያው ዶክተር አክሎግ ቢራራም፣ ይህ ዐይነቱ የፖሊሲ ርምጃ በተሞከረባቸው ሀገራት ውጤት እንዳላመጣ ያስረዳሉ፤ በምትኩ በምርት እድገት ላይ አተኩሮ በመሥራት፣ ኢኮኖሚውን ከገጠመው ችግር ለማውጣት እንደሚቻል ያመለክታሉ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ደግሞ፣ ከብሔራዊ ብዙኀን መገናኛዎች ጋራ በነበራቸው ቃለመጠይቅ፣ መንግሥት የውጭ ምንዛሬ ተመን ለውጥ ለማድረግ ሐሳብ እንደሌለው መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ኦክቶበር 18, 2024
ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ያሏትን ግቦች አደጋ ላይ የጣለው የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግንኙነት
-
ኦክቶበር 17, 2024
ከጥቅምቱ የአሜሪካ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የአይምሮ ጭንቀት
-
ኦክቶበር 16, 2024
የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ ዛሬ መጀመሩን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አስታወቁ
-
ኦክቶበር 16, 2024
ኢትዮጵያውያን ታዋቂ እንስቶች የከበሩበት ምሽት
-
ኦክቶበር 15, 2024
ወደ ሪፐብሊካን ታጋድል የነበረችው አሪዞና እንዴት 'ስዊንግ ስቴት' ልትሆን ቻለች?
-
ኦክቶበር 15, 2024
የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተጀምሯል