ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ አከፋፈል ለማስተካከል ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋራ እያደረገቻቸው ባሉ ድርድሮች፣ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም አንዱ ኢኮኖሚያዊ መፍትሔ ተደርጎ በምክረ ሐሳብ ደረጃ ስለመቅረቡ ይገለጻል፡፡ ምክረ ሐሳቡ ለዓመታት ሲቀርብ እንደቆየ ያወሱት የኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት አማካሪው አቶ ያሬድ ኀይለ መስቀል፣ መንግሥት ግን ሳይስማማበት የቆየ ጉዳይ ስለመኾኑ ይናገራሉ፡፡ ይኹንና ባለፉት አምስት ዓመታት፣ ብሔራዊ ባንክ የወሰዳቸው የብርን የመግዛት አቅም የማዳከም ርምጃዎች፣ ከመፍትሔ ይልቅ ለዋጋ ንረት እና ተያያዥ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ዳርገዋል፤ ይላሉ፡፡ የምጣኔ ሀብት ባለሞያው ዶክተር አክሎግ ቢራራም፣ ይህ ዐይነቱ የፖሊሲ ርምጃ በተሞከረባቸው ሀገራት ውጤት እንዳላመጣ ያስረዳሉ፤ በምትኩ በምርት እድገት ላይ አተኩሮ በመሥራት፣ ኢኮኖሚውን ከገጠመው ችግር ለማውጣት እንደሚቻል ያመለክታሉ፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ደግሞ፣ ከብሔራዊ ብዙኀን መገናኛዎች ጋራ በነበራቸው ቃለመጠይቅ፣ መንግሥት የውጭ ምንዛሬ ተመን ለውጥ ለማድረግ ሐሳብ እንደሌለው መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ
-
ጁላይ 22, 2024
የነዋሪዎች አስተያየት በፕሬዝደንት ባይደን ውሳኔ ላይ
-
ጁላይ 18, 2024
ጄ. ዲ. ቫንስ “አሜሪካ ትቅደም” መሪ ቃላቸው እንደሆነ አስታወቁ