በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ


የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:41 0:00

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ

በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉት ግጭቶች፣ ከፍተኛ ሰብአዊ ሥቃይ እያስከተሉ መሆኑ በእጅጉ እንዳሳሰበው የገለጸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ፣ በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጠይቋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጆሴ ማሲንጋ ሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት የጀመሩበትን 120ኛ ዓመት አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደብዳቤ የጻፉት፣ አገራቸው በኢትዮጵያ ሰላም እና ልማት እንዲረጋገጥ ድጋፍ እያደረገች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በአምባሳደሩ ስለተጻፈው ደብዳቤ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ የሰጡት፣ በኤምባሲው የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ኃላፊ ናዮሚ ፌሎውስ፣ በኢትዮጵያ ያሉት ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ አገራቸው ጥረት እንደምታደርግ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG