በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በአዋጁ መቀጠል ላይ የሚጋጩ ሃሣቦች አሉ


በአዋጁ መቀጠል ላይ የሚጋጩ ሃሣቦች አሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:49 0:00

በአማራ ክልል ላይ ተጥሎ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ለአራት ተጨማሪ ወራት እንዲራዘም ፓርላማው ዛሬ ወስኗል።

ላለፉት ስድስት ወራት ተፈፃሚ ሆኖ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲራዘም ለምክር ቤቱ ጥያቄ ያቀረቡት የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌድዮን ቲሞጢዎስ የአዋጁን ጊዜ ማራዘም ያስፈለገው ከአማራ ክልል በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም ያሉ “አንዳንድ አዝማሚያዎችና የፀጥታ ሥጋቶችንም ታሳቢ በማድረግ” መሆኑን ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ በተጨማሪም “በዕቅድ የተያዙ” ያሏቸውን “ቀሪ ሥራዎችንም ለመሥራት” እና “የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ጠቅላይ ዕዙ አዋጁ ቢራዘም ለህዝብ ደኅንነትና ሠላም በጣም ጠቃሚና አስፈላጊ መሆኑን በመደምደሙ” እንደሆነ አክለው ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ግን የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታው መራዘሙ እንዳሳዘናቸው አስተያየቶቻቸውን ለአሜሪካ ድምፅ የሰጡ የክልሉ ነዋሪዎች ገልፀዋል።

አዋጁ በክልሉ “አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን እንደረዳ” መንግሥት ተናግሯል።

XS
SM
MD
LG