ሞያዊ ሥልጠና ያገኙ የአፍሪካ የምግብ አዘጋጅ ኩባኒያዎች ገቢያቸው እና የግብርና ምርት አቅርቦታቸው ጥራት እየተሻሻለ መሆኑ ተገለፀ።
የአፍሪካን ገበሬዎች እና የምግብ አዘጋጆች በቅርብ ዓመታት እየታየ ያለው አየር ንብረት ለውጥ ጎድቷቸዋል። ይህም የምግብ አምራች ገበሬዎቹን ብቻ ሳይሆን የምግብ አዘጋጅ ኩባኒያዎች የሚያስፈልጋቸው አቅርቦት ከጊዜ ወደ ጊዜ አስተማማኝ እንዲያጣ እያደረገ ነው። በአፍሪካ ሀገሮች የምግብ ዋስትና ዙሪያ የሚሠራ አንድ ድርጅት እንደሚለው፣ የአፍሪካ ገበሬዎች እና በምግብ ዝግጅት ላይ የተሰማሩ ኩባኒያዎች ከተሰበሰበ በኋላ ተበላሽቶ የሚወድቀውን የምግብ ምርት ለመቀነስ፣ ከአየር ንብረት ለውጡ ጋር ለመለማመድ እንዲሁም የተሻለ መሰረተ ልማት ለመፍጠር ጥረት እያደረጉ ናቸው፡፡ መሐመድ ዩሱፍ ከናይሮቢ ያጠናቀረው ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።