በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኤፍራታ ግድምና ጅሌ ጥሙጋ ተረጋግተዋል


ኤፍራታ ግድምና ጅሌ ጥሙጋ ተረጋግተዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:40 0:00

ለሰብዓዊና ቁሣዊ ጉዳቶች ምክንያት ለሆኑ የሰሜን ሸዋና የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞኖች ግጭቶች ዘላቂ መፍትኄ ለማግኘት እየጣሩ መሆናቸውን አባገዳዎች የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ከሣምንት በፊት ተቀስቅሶ የነበረ በመሣሪያ የታጀበ ግጭት በሃገር ሽማግሎቹ ጥረት በርዶ አካባቢው መረጋጋቱ ተገልጿል።

በሰሜን ሸዋ ዞን ኤፍራታ ግድም ወረዳ አላላ በተባለች የገጠር ቀበሌና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጅሌ ጥሙጋ ባለፈው ታህሳስ 25 እና 26/2016 ዓ.ም ወደ ተኩስ የተሸጋገረ ግጭት ተፈጥሮ እንደነበር ታውቋል።

ወደ አጣዬ ከተማም ተሸጋግሮ እንደነበረ የተገለፀው ግጭት በህይወት፣ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።

የሰሜን ሸዋ ዞን አገር ሽማግሌ በለው አራምዴ “የኖሩ” የሚሏቸው ችግሮች በሰበብ አስባብ ወደ ግጭትነት እንደሚቀጣጠሉ ጠቁመዋል።

XS
SM
MD
LG