በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

“ረሃቡ በትምህርት ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው” የትግራይ ክልል የት/ቢሮ


“ረሃቡ በትምህርት ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው” የትግራይ ክልል የት/ቢሮ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:05 0:00

በትግራይ ክልል በረሃብ ምክንያት 223 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎች “ትምህርታቸውን ከማቋረጥ ቋፍ ላይ ናቸው” ሲል የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለፀ::

“የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብሩን በመጀመር ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ ይገባል” ሲልም አሳስቧል::

በክልሉ ኢሮብ ወረዳ በጦርነቱ እና በድርቁ ከ3600 በላይ ተማሪዎች እንዲሁም በአፅቢ ወረዳ አስር ሺሕ የሚጠጉ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን የአካባቢው አመራሮች ገልጸዋል::


የተባበሩት መንግሥታት ዕርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (UN ኦቻ) ትናንት ባወጣው ሪፖርት በበኩሉ በክልሉ 105 ትምህርት ቤቶች በተፈናቃዮች መጠለያነት መያዛቸውን ገልጿል::


በኢሮብ ወረዳ በአከባቢው የተፈጠረው ድርቅ ባስከተለው ረሃብ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ እያስገደደ መሆኑን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ኢያሱ ተስፋይ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል::

XS
SM
MD
LG