በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ስምምነቱ በቀጣናው ሊኖረው የሚችለው ተጽዕኖ - የተንታኞች አስተያየት


ስምምነቱ በቀጣናው ሊኖረው የሚችለው ተጽዕኖ - የተንታኞች አስተያየት
please wait

No media source currently available

0:00 0:11:47 0:00

በኢትዮጵያና በሶማሊላንድ መሪዎች የተፈረመው ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበት የመግባቢያ ሠነድ ሶማሊያን ጨምሮ ከሌሎች ጎረቤት ሃገሮች ጋር ባላት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል በአሜሪካ ኢንዲያና ዩንቨርስቲ የህገ መንግስታዊ ዲሞክራሲ ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ ፋንታው ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል፡፡፡

“ስምምነቱ የኢትዮጲያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ የሚሆነው ብስለት ያላቸው ዲፕሎማሲያዊ ስራዎችን መስራት ከተቻለ ብቻ ነው” ሲሉም አክለዋል፡፡

የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና በበኩላቸው “እንደ አየር መንገድ ያሉትን ትላልቅ ሃገራዊ ተቋማት የስምምነቱ አካል ማድረግ በቂ ዉይይት የሚጠይቅ ነው” ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል የመግባቢያ ስምምነቱን የተቃወመው ሶማሊያ መንግስት በኢትዮጵያ የሚገኙትን አምባሳደሩን ጠርቷል፡፡

XS
SM
MD
LG