በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የትግራይ ተቃዋሚዎች በረሃብ ምላሽ ጉዳይ ባለሥልጣናቱን ወቀሱ


የትግራይ ተቃዋሚዎች በረሃብ ምላሽ ጉዳይ ባለሥልጣናቱን ወቀሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:18 0:00

“የትግራይ ክልል ባለሥልጣናት ከአንድ ወር በላይ በስብሰባ ተጠምደዋል” ሲሉ አራት የክልል ፓርቲዎች ወቀሳ አሰምተዋል።

ዓረና ትግራይ፣ ባይቶና፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ እና ውድብ ናፅነት የሚባሉ የክልሉ ፓርቲዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ በተራዘመ ስብሰባቸው ምክንያት ባለሥልጣናቱ ለረሃቡ ምላሽ ካለመስጠታቸው በተጨማሪ መንግሥታዊ አገልግሎቶችም መስተጓጎላቸውን ተናግረዋል።

የክልሉ የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽነር፤ ዶ/ር ገብረህይወት ገብረእግዚአብሔር ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ “ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተቃዋሚዎቹ ፓርቲዎች የተሳተፉበት ኮሚቴ አዋቅሮ ለረሃቡ አስቸኳይ ምላሽ ለመስጠት ጥረት እያደረገ ነው” ብለዋል።

ትግራይ ውስጥ በረሃብ ምክንያት ሰው እየሞተ መሆኑን “ኪዳን ለሥር ነቀል ለውጥ” በሚል የጋራ ጥላ ሥር በተደራጁት አራቱ ፓርቲዎች ዓረና ትግራይ፣ ሳልሳይ ወያነ፣ ባይቶና እና ውድብ ናፅነት ተናግረዋል።

ረሃቡን ዓለም እንዲያውቀውና ትኩረት እንዲያገኝ አለመደረጉን የዓረና ለዴሞክራሲ እና ሉአላዊነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገብረሥላሴ አመልክተው ለጋሾች ዘንድ ‘ወደ ክልሉ የሚላክ እርዳታ ይዘረፋል’ የሚል ሥጋት መኖሩ ችግሩን እንዳባባሰው ገልፀዋል።

XS
SM
MD
LG