በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጋዛውያንን ኀዘን የተጋሩት የናዝሬት ክርስቲያኖች የገናን የበዓል መሰናዶ አቀዝቅዘዋል


የጋዛውያንን ኀዘን የተጋሩት የናዝሬት ክርስቲያኖች የገናን የበዓል መሰናዶ አቀዝቅዘዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:58 0:00

እንደ ክርስትና እምነት አስተምህሮ፣ የእስራኤሏ ናዝሬት፣ ለድኅነት ዓለም የመጣው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የተፀነሰባት፣ የተወለደባት እና ያደገባት አነስተኛ ከተማ ናት፡፡ በከተማዋ የሚኖሩ ክርስቲያኖች፣ የፊታችን ሰኞ የሚውለውን የዘንድሮ የገና በዓል አከባበር፣ ከወትሮው ቀዘዝ አድርገውታል። ይኸውም፣ በእስራኤል ወታደራዊ ጥቃት ውስጥ ለሚገኙት የጋዛ ፍልስጥኤማውያን ድጋፋቸውን ለመግለጽ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡

ቪኦኤ ያነጋገራቸው የከተማዋ አብያተ ክርስቲያናት አባቶች፣ "በዚኽ ጊዜ የበዓል ስሜት ሊኖር አይችልም፤” ብለዋል። ነጋዴዎች በበኩላቸው፣ እስራኤል እና ሐማስ በሚያሒዱት ጦርነት ምክንያት፣ ጎብኚዎችም ኾኑ ምእመናን ስለቀሩ ገበያቸው በጣም እንደቀዘቀዘባቸው ያማርራሉ።

ሄንሪ ዊልኪንስ ከእስራኤል ናዝሬት ያጠናቀረው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል ቆንጅት ወደ ዐማርኛ መልሳዋለች።

XS
SM
MD
LG