በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በፈረስ ቤት ከተማ ለ5ኛ ቀን በቀጠለው ግጭት በድሮን ጥቃት ጉዳት መድረሱ ተገለጸ


በፈረስ ቤት ከተማ ለ5ኛ ቀን በቀጠለው ግጭት በድሮን ጥቃት ጉዳት መድረሱ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:20 0:00

በዐማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ ፈረስ ቤት ከተማ አካባቢ፣ ባለፈው ሰኞ የተቀሰቀሰው ውጊያ፣ ዛሬም ቀጥሎ እንደዋለ፣ የአካባቢው የመረጃ ምንጮች ተናግረዋል፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ትላንት ረቡዕ ምሽት በድሮን እንደኾነ በገለጹት ከባድ መሣሪያ፣ የሰው ሕይወት ማለፉንና የአካል ጉዳት መድረሱን፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል፡፡

ውጊያው ዛሬም ቀጥሎ እንደዋለ ምንጮቹ ጠቁመው፣ ከከባድ መሣሪያ ጥቃት ራሳቸውን ለመከላከል፣ በርካቶች በዱር እና በገደል አካባቢዎች ለመደበቅ እንደተገደዱ ገልጸዋል፡፡

XS
SM
MD
LG