በሐዲያ ዞን መምህራን ሥራ በማቆማቸው መቶ ሺሕዎች ከትምህርት እንደራቁ ተገለጸ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሐዲያ ዞን፣ ለወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው መምህራን ሥራ በማቆማቸው እስከ አሁን የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ሒደት እንዳልተጀመረ፣ ወላጆች እና መምህራን ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። ትምህርት ባልተጀመረባቸው በዞኑ ስምንት ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች፣ ከትምህርት ቤት ውጪ እንደኾኑ፣ ቅሬታ አቅራቢዎቹ አማርረዋል። የዞኑ እና የክልሉ ባለሥልጣናት ስልካቸውን ስለማያነሡ፣ ምላሽ እና አስተያየታቸውን ለማካተት አልቻልንም።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
በማላዊ ለአሳዳጊ አልባ ሕፃናት መጠጊያ የኾነው ማዕከል
-
ጁላይ 27, 2024
በጠፈር ምርምር ትምህርት መርሐ ግብር የተመረቁ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ