በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ባለፉት ስድስት ወራት ቁጥራቸው የበዛ የዐማራ ተወላጆች እንደተገደሉ የፍጅት መከላከል ድርጅቱ ገለጸ


ባለፉት ስድስት ወራት ቁጥራቸው የበዛ የዐማራ ተወላጆች እንደተገደሉ የፍጅት መከላከል ድርጅቱ ገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:23:25 0:00

በኢትዮጵያ በልዩ ልዩ አካባቢዎች በሚኖሩ የዐማራ ተወላጆች ላይ፣ በታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች እየደረሱ ናቸው በተባሉ ጥቃቶች፣ ካለፈው ዓመት ሚያዝያ እስከ መስከረም ባለው ጊዜ፣ 11ሺሕ ሰዎች እንደተገደሉና ከ100ሺሕ በላይ ሰዎች ደግሞ እንደታሰሩ፣ “የዘር ፍጅት ቅድመ መከላከል በኢትዮጵያ” የተሰኘ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት አስታውቋል።

ለሁለት ዓመት በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሔደው ጦርነት በስምምነት ከቆመ በኋላ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በፋኖ ታጣቂ መካከል እየተካሔደ ባለው ግጭት ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱ፣ ከፌዴራልም ኾነ ከክልሉ መንግሥት እስከ አሁን የተገለጸ ቁጥር ባይኖርም፣ ግጭቱን ተከትሎ በክልሉ በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ፣ በዐማራ ክልል ብቻ 764 ሰዎች እንደታሰሩ መርማሪ ቦርዱ ባለፈው ወር አስታውቆ ነበር።

ድርጅቱ ባአወጣው ሪፖርት ላይ፣ ከፌዴራልም ኾነ ከዐማራ ክልል መንግሥት ምላሽ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም፣ ቀጥተኛ ምላሽ አላገኘንም።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በዐማራ ክልል እየተካሔደ ባለው ግጭት፤ በዐማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ነው ያለውን የእስር ዘመቻ እና ሌሎችም የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን በተለያዩ ጊዜያት አውግዟል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ሌሎች ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት በተለያዩ ጊዜያት በሚያወጧቸው ሪፖርቶች፣ በዐማራ ተወላጆች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንደሚያሳስቧቸው ገልጸዋል።

ስመኝሽ የቆየ የተቋሙን ዳይሬክተር ዶ/ር ሰናይት ደረጀን አነጋግራ ያሰናዳችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG