በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጉራጌ እና በቀቤና ብሔረሰቦች ግጭት ከመቶ በላይ ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ ተገለጸ


በጉራጌ እና በቀቤና ብሔረሰቦች ግጭት ከመቶ በላይ ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:37 0:00

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ፣ በጉራጌ እና በቀቤና ብሔረሰቦች አባላት መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተጠረጠሩ 123 ሰዎች እንደተያዙ፣ የዞኑ አስተዳዳር አስታወቀ።

የአስተዳደሩ ሓላፊ አቶ ኤልያስ ሽበርጋ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል፣ በግጭቱ አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባልን ጨምሮ አራት ሰዎች እንደተገደሉ አረጋግጠው፣ ከአንድ መቶ በላይ የከተማው ነዋሪዎች ደግሞ እንደቆሰሉ ተናግረዋል።

አሁን ላይ የወልቂጤ ከተማ፣ መረጋጋት እንደሚታይበትና ወደ መደበኛ እንቅስቃሴውም እንደተመለሰ አቶ ኤልያስ ሽበርጋ ገልጸው፣ ከውድመት የተረፉ የመንግሥት ቢሮዎች እና የግለሰብ ሀብቶች በመጣራት ላይ ናቸው፤ ብለዋል።

የወልቂጤ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ ከተማው እየተረጋጋ ቢኾንም፣ ስጋት መኖሩን አመልክተዋል፡፡

XS
SM
MD
LG