በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና እየተሰጠ ነው


በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና እየተሰጠ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:49 0:00

በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና እየተሰጠ ነው

በትግራይ ክልል፣ ለአራት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው፣ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. መስጠት ተጀምሯል፡፡
በዚኽ ፈተና፣ በ2012 ዓ.ም. መፈተን የሚገባቸው ከ9ሺሕ500 በላይ ተማሪዎችም ተቀምጠዋል፤ ሲሉ፣ የኢትዮጵያ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዲሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሓላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ በበኩላቸው፣ ፈተናው፣ በዚኽ ዓመት ለሦስት ጊዜያት እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ ይኸውም፣ በክልሉ የትምህርት ጊዜ ያለፈባቸውን ተማሪዎች ለማካተት በሚል እንደኾነ አስረድተዋል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG