በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የምግብ አቅርቦት በፍጥነት ጋዛ እንዲያደርስ የዓለም የምግብ ፕሮግራም ጠየቀ


ፍልስጤማውያ ዛሬ መስከረም 27/ 2016 ዓ.ም በእስራኤል ባደረሰችው ጥቃት በወደኡ በጋዛ ከተማ በዋታን ግንብ አቅራቢያ በሚገኑ የሕንፃ ፍርስራሾች መካከል ሲንቀሳቀሱ።
ፍልስጤማውያ ዛሬ መስከረም 27/ 2016 ዓ.ም በእስራኤል ባደረሰችው ጥቃት በወደኡ በጋዛ ከተማ በዋታን ግንብ አቅራቢያ በሚገኑ የሕንፃ ፍርስራሾች መካከል ሲንቀሳቀሱ።

የጋዛ ሰርጥን የሚያስተዳድሩት የሃማስ ቡድኖች በቴል አቪቭ እና በዙሪያው በሚገኙ የእስራዔ ከተሞች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ እስራኤል በጋዛ ላይ በፈፀመች የዓየር ጥቃት ምክኒያት የምግብ የርዳታ ምግብ ማስተላለፊያ ኮሪደሮች ክፍት እንዲኾኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም የምግብ ፕሮግራም ጥሪ አቀረበ።

ግጭቱ እየጠነከረ ከሄደ ለጦርነት ተጋላጭ የኾኑ ህጻናት እና ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ሲቪሎች አስፈላጊ የሆኑ የምግብ አቅርቦቶችን ለማግኘት ችግር እንደሚያጋጥማቸው፣ መቀመጫውን ሮም ያደረገው የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታውቋል።

ድርጅቱ ባወጣው በዚህ መግለጫ፣ ለተጎዱት አካባቢዎች የሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ እንዳይደናቀፍ እና የምግብ አቅርቦት ማረጋገጥን ጨምሮ ሁሉም አካላት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መርሆዎችን እንዲያከብሩ ጠይቋል።

"ተመድ በየወሩ 350 ሺሕ ለሚኾኑ ፍልስጤማውያን ቀጥተኛ የምግብ ርዳታ ይሰጣል ፣እንዲሁም ከሌሎች አጋሮች ጋራ በመተባበር ለሌሎች ወደ 1 ሚሊዮን ለሚጠጉ ፍልስጤማውያን ርዳታ ያቀርባል" ያለው የድርጅቱ መግለጫ፣ አኹንም ለተፈናቀሉ ወይም በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች ምግብ ለማቅረብ ዝግጁ መኾኑን አስታውቋል።

መግለጫው አክሎም "ጉዳቱ በደረሰባቸው አካባቢ የሚገኙ አብዛኛዎቹ ሱቆች ሊኖራቸው የሚችለው ለአንድ ወር የሚበቃ የምግብ ክምችን ነው፣ ያም ቢኾን ጦርነቱ ሊራዘም ይችላል የሚል ስጋት ያላቸው ሰዎች ያለውን ምግብ አብዝተው ሊሸምቱት ስለሚችሉ ክምችቱ በፍጥነት ሊሟጠጥ ይችላል" ብሏል። በተደጋጋሚ የኤሌትሪክ ሓይል መቆራረጥ ምክኒያትም ምግቦች ሊበላሹ እንደሚችሉ ድርጅቱ ስጋቱን አጋርቷል።

እሥራዔል እሁድ እለት ጋዛን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት ማድረሷን ቀጥላለች። እሥራዔል ጥቃቱን የጀመረችው፣ የሃማስ ተዋጊዎች እሥራዔልን ከጋዛ የሚለየውን አጥር ጥሰው በመግባት፣ ባለፉት አስርት ዓመታት ያልታየ ጥቃት በማድረሳቸው እና ከ700 በላይ ሰዎችን ገድለው በደርዘን የሚቆጠሩትን ደግሞ በማገታቸው ነው።

ጥቃቱን ተከትሎ የእሥራዔል ጦር፣ በጋዛ ዙሪያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማሰማራቱን አስታውቋል። 2.3 ሚሊየን ፍልስጤማውያን በሚኖርባት ጠባብ ሰርጥ፣ እሥራዔል ከፍተኛ መጤን ያለው ጥቃት ልታደርስ ትችላለች የሚለው ስጋትም እያየለ መጥቷል።
እሥራዔል እስካሁን ባደረገችው የአየር ድብደባ፣ ከ400 በላይ ፍልስጤማውያንን መግደሏን አስታውቃለች።
በእየሩሳሌም የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ፣ አሁን በእሥራዔል ያለው ሁኔታ ተለዋዋጭ መሆኑን በመጥቀስ፣ ወደ እሥራዔል ለሚጓዙ የአሜሪካ ዜጎች የጉዞ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። በተጨማሪም በእሥራዔል የሚኖሩ የአሜሪካ ዜጎች እርዳታ ካስፈለጋቸው በቅርባቸው የሚገኘውን ኤምባሲ ወይም የቆንፅላ ፅህፈት ቤት እንዲያነጋግሩ አመልክቷል።
የጉዞ ማስጠንቀቂያው አክሎ፣ ከእሥራዔል መውጣት የሚፈልጉ እና ደህንነታቸው በተጠበቀ መልኩ መንቀሳቀስ የሚችሉ፣ አስቀድመው ድንበር ማቋረጫዎች ላይ ያለውን ሁኔታ እንዲያጣሩ እና ወደ ቤን ጉሪዮን የአየር ማረፊያ ከማምራታቸው በፊት በረራዎች አለመሰረዛቸውን እንዲያረጋግጡም አሳስቧል።
የእስራኤል የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሚኒስትር ሮን ዴርመር፣ በሃማስ ከታገቱት መካከል የአሜሪካ ዜጎች እንደሚገኙበት ቢያስታውቁም፣ ስለማንነታቸው ዝርዝር መረጃም ሆነ፣ በጥቃቱ ምናልባት ስለተገደሉ አሜሪካውያን ዝርዝር መረጃ አልሰጡም።
ዴርመር ከሲኤንኤኑ 'ስቴት ኦፍ ዩኒየን' ጋር ባደረጉት ቆይታ ሲናገሩ "አዝናለሁ እሱን መናገር አልችልም። እሥራዔል ውስጥ ጥምር ዜግነት ያላቸው ብዙ ሰዎች አሉ። በርካታ ሊሆኑ እንደሚችሉ እጠራጠራለሁ። ነገር ከዚህ ዘግናኝ ጥቃት በኃላ ሁሉንም መረጃ ገና ለማጣራት እየሞከርን ነው። ዘመዶቻቸው የተገደሉባቸው እና የታገቱባቸው ሰዎች በአስቸኳይ ማወቅ እንዲችሉ መረጃውን ይፋ እናደርጋለን" ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን እሥራዔል ውስጥ ይኖሩ የነበሩ፣ ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ አውሮፓውያን እና አሜሪካውያን መሞታቸው ወይም መታገታቸው ተዘግቧል።

መሞታቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ውስጥ ሦስት እንግሊዛውያን፣ አንዲት ፈረንሳዊት እና ሁለት ዩክሬናውያን ሲገኙበት ጀርመን በሃማስ ከታገቱ ሰዎች ውስጥ ዜጎቿ እንደሚገኙበት አስታውቃለች።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG