በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዐማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎት እንደተቋረጠ ነዋሪዎች ገልፁ


በዐማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎት እንደተቋረጠ ነዋሪዎች ገልፁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:15 0:00

በዐማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎት እንደተቋረጠ ነዋሪዎች ገልፁ

በዐማራ ክልል፣ በምዕራብ እና ምሥራቅ ጎጃም ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች፣ ከትላንት ማክሰኞ ከቀትር በኋላ ጀምሮ፣ የስልክ አገልግሎት በመቋረጡ፣ የዘመዶቻቸውን ደኅንነት ማወቅ እንዳልቻሉ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው፣ የባሕር ዳር እና የዐዲስ አበባ ከተሞች ነዋሪዎች፣ በምሥራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ማርቆስ ከተማ እና በምዕራብ ጎጃም ዞን በፍኖተ ሰላም፣ በደንበጫ እና በዙሪያው፣ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ የስልክ አገልግሎት እንደማይሠራ አረጋግጠናል፤ ብለዋል፡፡

ሰሞኑን፣ ዳግም በተቀሰቀሱት ግጭቶች፣ በየዕለቱ ከቤተሰቦቻቸው ጋራ በስልክ ስለ ደኅንነታቸው እንደሚጠያየቁ የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ አሁን ላይ ግንኙነቱ መቋረጡ እንዳስጨነቃቸው ተናግረዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬ ሕይወት ታምሩን፣ በዋትሳፕ መተግበሪያ መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀናቸው፣ ለቦርድ ስብሰባ ውጭ ሀገር እንደሚገኙና ምላሽ የሚሰጡንን ሰዎች እንደሚመድቡ በመልዕክታቸው ገልጸውልናል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG