በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የስፔይን እግር ኳስ ተጫዋች የፌዴሬሽኑን ፕሬዚዳንት ከሰሰች


ፋይል - የሴቶች እግር ኳስ ጨዋታ አሸናፊ የሆነው የስፔይን ቡድን ተጫዋች ጄኒ ሄርሜሶ ዋንጫውን ስታነሳ - ነሐሴ 21፣ 2023
ፋይል - የሴቶች እግር ኳስ ጨዋታ አሸናፊ የሆነው የስፔይን ቡድን ተጫዋች ጄኒ ሄርሜሶ ዋንጫውን ስታነሳ - ነሐሴ 21፣ 2023

ዘንድሮ የዓለም የሴቶች እግር ኳስ ጨዋታ አሸናፊ የሆነው የስፔይን ቡድን ተጫዋች ጄኒ ሄርሜሶ የአገሪቱን የእግር ኳስ የፌድሬሽን ፕሬዚዳንት በወሲብ ትንኮሳ እንደምትከሳቸው የስፔይን አቃቤ ህግ ዛሬ አስታወቀ፡፡

ሄርሜሶ ክሱን የመሠረተቸው የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሉዊስ ሩቤለስ በሴቶቹ የእግር ኳስ ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ደስታቸውን ለመግለጽ ያለፈቃድዋ ከንፈሯ ላይ በመሳማቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡

ባላፈው ነሀሴ ወር መገባደጃ ላይ፣ የአለም እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል ፊፋ፣ የፕሬዚዳንቱ "የዲሲፕሊን ጉዳይ እስኪታይ ድረስ" በሩቤለስ ላይ የ90 ቀናት እገዳ ጥሏል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሉዊስ ሩቤለስ የተፈጠረው መሳሳም በፈቃደኝነት ላይ የተደረገ መሆኑን በመግለጽ ከሥልጣናቸው ለመነሳት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የስፔይን ፖለቲከኞች እና አንዳንዶቹ የአገሪቱ ዝነኛ የእግር ኳስ ክለቦች የፕሬዚዳንቱን ድርጊት አውግዘዋል፡፤

የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ሌሎች ሁለት ኃላፊዎች ድርጊቱን በመቃወም በገዛ ፈቃዳቸው ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸው ተገልጿል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG