በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

እንደራሴዎቹ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋራ እንዳይወያዩ መከልከላቸውን ገለጹ


እንደራሴዎቹ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋራ እንዳይወያዩ መከልከላቸውን ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:40 0:00

እንደራሴዎቹ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋራ እንዳይወያዩ መከልከላቸውን ገለጹ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአማሮ ኮሬ ዞን እንደራሴዎች፣ ከመረጣቸው ሕዝብ ጋራ ውይይት እንዳያደርጉ መከልከላቸውን ገለጹ።

የዞኑ አስተዳዳሪ በበኩላቸው፣ በዞኑ የጸጥታ ችግር እንዳለና ለሕዝብ ተወካዮቹም ደኅንነት ሲባል፣ ችግሩ እስኪፈታ ድረስ እንዲታገሡ አሳወቅናቸው እንጂ እንዳይወያዩ አልከለከልናቸውም፤ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

በጉዳዩ ለቪኦኤ አስተያየታቸውን የሰጡት በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር አንዱዓለም ነጋ፤ የሕዝብ እንደራሴዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ ሁኔታ የመረጣቸውን ሕዝብ የማወያየት መብት እንዳላቸው ተናግረዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG