በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዐማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ቀጥሏል


በዐማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ቀጥሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:06 0:00

አብዛኛው የዐማራ ክልል አካባቢዎች፣ ወደ ሰላማዊ ኹኔታ ተመልሰው መደበኛ እንቅስቃሴ ቢጀመርም፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የጨረቃ አካባቢ እና በምሥራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ ዐማኑኤል ከተማ፣ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል፣ የተኩስ ልውውጥ እየተካሔደ እንደሚገኝ፣ ነዋሪዎች ለቪኦኤ ገለጹ።

በተኩስ ልውውጡ፣ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን፣ ነዋሪዎቹ አክለው ተናግረዋል። በሌላ በኩል፣ ግጭቱ፣ የሰብአዊ ርዳታንና በቅርቡ የተከሠተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት እንዳስተጓጎለው፣ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ቢሮ አስታውቋል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን ዘገባ ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG