በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በምሥራቅ ቦረና ዞን ዐዲስ አደረጃጀት የጎሮ ዶላ ወረዳ ተቃውሞ ተባብሶ እንደቀጠለ ተገለጸ


በምሥራቅ ቦረና ዞን ዐዲስ አደረጃጀት የጎሮ ዶላ ወረዳ ተቃውሞ ተባብሶ እንደቀጠለ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:58 0:00

በምሥራቅ ቦረና ዞን ዐዲስ አደረጃጀት የጎሮ ዶላ ወረዳ ተቃውሞ ተባብሶ እንደቀጠለ ተገለጸ

በኦሮሚያ ክልል፣ በቀድሞ አደረጃጀት በጉጂ ዞን ሥር የነበረችው ጎሮ ዶላ ወረዳ፣ በዐዲሱ አደረጃጀት ሳቢያ የተነሣውና ላለፉት ስድስት ወራት እልባት ሳያገኝ የሰነበተው ችግር አሁን ተባብሶ፣ በወረዳዋ፣ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሥራ ከአቆሙ 45 ቀናት እንደተቆጠሩ፣ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የጎሮ ዶላ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጌቱ ጩሉቄ፣ በወረዳዋ በሥራ ላይ የሚገኙት ከአንድ የእጅ ጣት ያልበለጡ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ብቻ እንደኾኑ ገልጸዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ፣ ከምሥራቅ ቦረና እና ከኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መልስ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG