በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለዐማራ ክልል ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ ጥረት እየተደረገ እንደኾነ ደመቀ መኰንን ተናገሩ


ለዐማራ ክልል ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ ጥረት እየተደረገ እንደኾነ ደመቀ መኰንን ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:58 0:00

መንግሥት፣ በዐማራ ክልል በአገር መከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂ መካከል የተስፋፋውን ግጭት፣ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ፣ አቶ ደመቀ መኰንን ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኰንን፣ በዐዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት፣ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ደመቀ በማብራሪያቸው፣ መንግሥት እስከ አሁን በወሰዳቸው ርምጃዎች፣ ለውጥ እንደመጣ ገልጸዋል

ከአቶ ደመቀ የመግቢያ ንግግር በኋላ፣ ለብዙኀን መገናኛ ዝግ በነበረው በዚኹ ውይይት ላይ ስለተነሡ ዝርዝር ጉዳዮች፣ እስከ አኹን የወጣ መረጃ የለም፡፡

በአንጻሩ፣ መንግሥት፣ ለዐማራ ክልል ችግር ሰላማዊ መፍትሔን ከመሻት ይልቅ፣ የኀይል ርምጃን ተመራጭ አድርጓል፤ ሲሉ የሚተቹ አካላት አሉ፡፡

በርካታ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ አካላትም፣ አሳስቦናል ያሉት በክልሉ የተስፋፋው ግጭት፣ በውይይት እንዲፈታ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG