በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በዓመቱ ውስጥ ከሩብ ሚሊዮን በላይ የዜጎችን አቤቱታ እንደተቀበለ ገለጸ


የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በዓመቱ ውስጥ ከሩብ ሚሊዮን በላይ የዜጎችን አቤቱታ እንደተቀበለ ገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:19 0:00

የኢትዮጵያ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ ይፋ ባደረገው የ2015 ዓ.ም. የአፈጻጸም ሪፖርቱ፣ በዓመቱ በልዩ ልዩ ዘርፎች “ችግር ደርሶብናል፤” ያሉ፣ ከ277 ሺሕ በላይ ዜጎች፣ ለተቋሙ አቤቱታ እንዳቀረቡ አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ዋና እንባ ጠባቂ ዶር. እንዳለ ኀይሌ፣ ስለ ሪፖርቱ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ማብራሪያ፣ ዘንድሮ በዜጎች የቀረበው የአቤቱታ ብዛት፣ ካለፉት ዓመታት ጋራ ሲነጻጸር፣ ከፍተኛ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡

ተቋሙ፣ አቤቱታዎችን እየመረመረ ውሳኔ እንደሚሰጥ የጠቀሱት ዋና እንባ ጠባቂው፣ ውሳኔውን ባልተገበሩ የመንግሥት አስፈጻሚዎች ላይ፣ ክሥ እንደመሠረተም አመልክተዋል።

ዝርዝርን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG