በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሸዋ ሮቢት የጸጥታ ዘርፍ ሓላፊ ባልታወቁ ኃይሎች ተገደሉ


የሸዋ ሮቢት የጸጥታ ዘርፍ ሓላፊ ባልታወቁ ኃይሎች ተገደሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:34 0:00

በዐማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ዘርፍ ሓላፊ፣ ትላንት፣ ባልታወቁ ሰዎች እንደተገደሉ፣ የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡

የሓላፊውን መገደል ተከትሎ፣ ከተማዋ ባልተረጋጋ ስሜት ውስጥ እንደምትገኝ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

የሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው አጭር የኀዘን መግለጫ፣ የሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ሓላፊ አቶ አብዱ ሑሴን፣ መንግሥታዊ ሓላፊነታቸውን በመወጣት ላይ እያሉ ትላንት፣ ሰኔ 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 11:00፣ መገደላቸውን ገልጿል፡፡

ስለ ሟቹ ግለ ታሪክም ኾነ ስለ አሟሟታቸው፣ መግለጫው ያለው ነገር የለም፡፡ ብለዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG