በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የእምነት ተቋማትን በራሱ ላለማፍረስ ተስማማ 


የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የእምነት ተቋማትን በራሱ ላለማፍረስ ተስማማ 
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:08 0:00

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት፣ ሕዝበ ሙስሊሙ፥ በሸገር ከተማ እና በመላው የኦሮሚያ ክልል ለሚያቀርባቸው የመስጊድ ጥያቄዎች፣ በማስተር ፕላኑ መሠረት ምላሽ ለመስጠት መስማማቱ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ፣ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋራ፣ ሰፊ ውይይት መደረጉን አስታውቋል፡፡

በውይይቱም፣ የክልሉ መንግሥት፣ ከእንግዲህ መፍረስ ያለባቸውን አብያተ እምነት፣ ራሳቸው የእምነት ተቋማቱ እንዲያፈርሱ እንጂ፣ በራሱ ማፍረስ እንደሚያቆም መስማማቱ ተገልጿል፡፡

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ በመነጋገር እና በመወያየት ችግሩ መፍትሔ ማግኘቱን ገልጸዋል፡፡ ገብረ ሚካኤል ገብረ መድኅን ዝርዝር አለው፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ሰኔ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ፣ በሸገር ከተማ እየተካሔደ ባለው የመስጊድ ፈረሳ ጉዳይ፣ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዚዳንት አቶ ሺመልስ አብዲሳ ጋራ አምስት ሰዓታትን የፈጀ ሰፊ ውይይት ማድረጉን አስታውቋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተገኙት የም/ቤቱ ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ በሸገር ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ኹኔታ ብዛት ያላቸው መስጊዶች መፍረሳቸውን አመልክተው፣ አሁን ግን ችግሩ መፍትሔ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡

XS
SM
MD
LG