በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሱዳን የሚያወጣ ግብረ ኃይል ማቋቋሟን አስታወቀች


ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሱዳን የሚያወጣ ግብረ ኃይል ማቋቋሟን አስታወቀች
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:25 0:00

ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሱዳን የሚያወጣ ግብረ ኃይል ማቋቋሟን አስታወቀች

በሱዳን የሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች ውጊያ ከተጀመረበት እስከ ዛሬ ድረስ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንና የሌሎች ሀገራት ዜጎች ከሱዳን እንዲወጡ፣ ኢትዮጵያ ድጋፍ ማድረጓን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ዛሬ ኀሙስ፣ ሚያዝያ 20 ቀን 2015 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ፣ ለዚኹ ጉዳይ የተቋቋመ፣ የመንግሥት ኃይለ ግብር፣ በድንበር አካባቢ ተሠማርቶ እየሠራ መኾኑን ተናግረዋል፡፡

ቃለ አቀባዩ በዛሬው መግለጫቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ከሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች መሪዎች ጋራ በስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡አያይዘውም፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል፣ በታንዛኒያዋ ዛንዚባር ደሴት ላይ የሚደረገው ድርድር፣ በሒደት ላይ እንደኾነ ቢጠቅሱም፣ ከዚኽ ያለፈ ዝርዝር መረጃ አልሰጡም፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

XS
SM
MD
LG