በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦሮሚያ ክልል የልዩ ኃይል አደረጃጀትን ሥምሪት ማቆሙን አስታወቀ


የኦሮሚያ ክልል የልዩ ኃይል አደረጃጀትን ሥምሪት ማቆሙን አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:50 0:00

የልዩ ኃይል አባላትን ወደ ልዩ ልዩ የጸጥታ ተቋማት በማስገባት መልሶ የማደራጀት ተግባር በማከናወን ላይ መኾኑን የገለጸው የኦሮሚያ ክልል፣ የልዩ ኃይል አደረጃጀትን ሥምሪት ማቆሙን፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ አስታወቁ።

የክልሉን የጸጥታ ማስከበር ሥራም፣ የአገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ መረከባቸውን ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ መልኩ፣ የደቡብ እና የሶማሌ ክልሎችም፣ በፌዴራል መንግሥት የተላለፈውን የልዩ ኃይል መዋቅራዊ ለውጥ ውሳኔ በመተግበር ሒደት ላይ መኾናቸውን አስታውቀዋል፡፡

የልዩ ኃይል አባላቱ፣ በመደበኛ የጸጥታ ተቋማት ማለትም በሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በፌዴራል ፖሊስ ሠራዊት እና በክልሎች ፖሊስ ሠራዊት ውስጥ እንደሚካተቱ የየክልሎቹ አመራሮች አስረድተዋል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG